የሀይማኖት ፀሎት

6 months ago
69

የሀይማኖት ፀሎት
፭ ሁሉን የፈጠረ አንድ አምላክ 
በሚሆንበእግዚአብሔር አብ 
እናምናለን ሰማይና ምድርን የፈጠረ የሚታየውንና የማይታየውን ዓለም ሳይፈጠረ ከርሱ ጋር በነበረ የአብ አንድ ልጅ በሚሆን
በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለንከብርሐን የተገኘ ብርሐን ከእውነተኛ 
አምላክ የተገኘ እውነተኛ አምላክ
የተወለደ እንጂ ያተፈጠረ በባሕርዩ  ከአብ ጋር የሚተካከል ሁሉ በእርሱ የሆነ ያለ እርሱ ግን ምንም ምን የሆነ የለም በሰማይም ካለው በምድርም ካለው 
ያለርሱ ምንም ምን የሆነ የለም ስለኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን  ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍፁም ሰው ሆነ ደግሞ ስለኛ ተሰቀለ  በጴንጤናዊዉ 
በጲላጦስ ዘመን እርሱ መከራን ተቀበለ ሞተ ተቀበረ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ በክብር በምስጋና ወደ ሠማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ዳግመኛም 
በሕያዋንና በሙታን ላይ ለመፍረድ  በምስጋና ይመጣል ለመንግሥቱም 
ፍፃሜ የለውም በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እርሱ ጌት ሕይወትን የሚሰጥ
ከአብ የሠረፀ ከአብ ከወልድ ጋራ በአንድነት እንሰግድለታለን እናመሰግነዋለን
እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረ ነው ከሁሉም በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሠርዋት በአንዲት ክብርት ቤተ ክርስቲያን 
እናምናለን ኃጢያት በሚሠረይባት 
በአንዲት ጥምቀት እናምናለን የሙታንንምመነሳት ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውም
 ሕይወት ለዘላለሙ

፮ አሸናፊ እግዚአብሔር ሆይ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብለህ ትመሠገናለህ ምስጋናህም በሰማይ በምድር የመላ ነው ክርስቶስ ሆይ ላንተ እንሰግድልሃለን ሰማያዊ ከሚሆን ከቸር አባትህ ጋርኝ
አዳኝ ከሚሆን ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ  እንሰግድልሃለን ወደዚህ ዓለም መጥተህ አድነኸናልና

፯ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ አንዲት ስግደት እሰግዳለሁ ፫ ጊዜ በል
አንድ ሲሆን ሦስት ሦስት ሲሆኑ አንድ በአካል ሦስት ሲሆኑ በመለኮት አንድ ለሚሆኑ አምላክ ለሚሆን እሰግዳለሁ አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለድንግል ማርያምም እሰግዳለሁ
ዓለምን ሁሉ ለማዳን ሲል ኢየሱስ ክርስቶስ ለተሰቀለበት መስቀልም እሰግዳለሁ
መስቀል ኃይላችን ነው
ኃይላችን መስቀል ነው
የሚያጸናን መስቀል ነው
መስቀል ቤዛችን ነው
መስቀል የነፍሳችን መዳኛ ነው
አይሁድ ይክዱታል እኛ ግን እናምነዋለን ያመነው እኛም በመስቀሉ እንድናለን ድነናልም

፰ ለአብ ምስጋና ይገባል ለወልድም ምስጋና ይገባል ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል ፫ ጊዜ በል
አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም ምስጋና ይገባል። ለኢየሱስ ክርስቶስ መስቀልም ምስጋና ይገባል
ክርስቶስ በቸርነቱ ያስበን ዘንድ ዳግመኛም በመጣ ጊዜ እንድዳያሳፍረን ስሙን ለማመስገን ያነቃን ዘንድ እመቤታችን ፀሎታችንን አሳርጊልን ኃጢያታችንንም አስተሥርዪልን
በጌትልችን መንበር ፊት ፀሎታችንን አሳርጊልን
ይህንን ኅብስት ላበላን
ይህንንም ጽዋ ላጠጣን
ምግባችንንና ልብሳችንንም ላዘጋጀልን ኃጢያታችንንም ሁሉ ለታገሰልን
ክቡር ደሙን ቅዱስ ሥጋውን ለሰጠን እስከዚህችም ሰዓት ላደረሰን
ለእሱ ለልዑል እግዚአብሔር ፍፁም ምስጋና ይገባል ለወለደችው ለድንግልም ምስጋና ይገባል ለክቡር መስቀሉም ምስጋና ይገባል እግዚአብሔር ስሙ ፈጽሞ ይመሰገን ዘንድ ዘወትር በየጊዜያቱ በየሰዓቱ ምስጋና ይገባል

፱ እናታችን ማርያም ሆይ ሰላም ላንቺ ይሁን እያልን እንሰግድልሻለን እንማልድሻለን ከአዳኝ አውሬ ታድኝን ዘንድ ተማጽነንብሻል ስለ እናትሽ ስለ ቅድስት ሐና ብለሽ ስለ አባትሽ ስለ ቅዱስ ኢያቄም ብለሽ ድንግል ማኅበራችንን ዛሬ ባርኪልን
፲ አምላክን በድንግልና የወለደች የእመቤታችን የማርያም ፀሎት
ሉቃ ፩፡፵፮-፶፬
ማርያምም አለች ነፍሴ እግዚአብሔርን ታላቅ ታደርገዋለች መንፈሴም በመድኀኒቴ በእግዚአብሔር ደስ ይላታል
የባሪያይቱን መዋረድ አይቷልና እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል እርሱ ብርቱ የሚሆን ታላቅ ስራን ለእኔ አድርጓልና ስሙም ቅዱስ ነው ለሚፈሩትም ምሕረቱ ለልጅ ልጅ ነው ኃይልን በክንዱ አደረገ በልባቸው አሳብ የሚኮሩ ትዕቢተኞችን በታተናቸው ብርቱዎችንም ከዙፋናቸው አዋረዳቸው የተዋረዱትንም ከፍ ከፍ አደረጋቸው የተራቡትንም በቸርነቱ አጠገባቸው ባለጠጎችንም ባዶ እጃቸውን ሰደዳቸው ምሕረቱን እንዲያስብ እስራኤል ባሪያውን ተቀበለ ለአባቶቻችን ለአብርሃምና ለዘሩም እስከ ዘለዓለም ድረስ እንደተናገረው

Loading comments...