የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም

6 months ago
53

ማክሰኞ የሚጸለይ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ምስጋና።
ሁለተኛ ክፍል።

፩ የመመኪያችን ዘውድ የድኅነታችን መጀመሪያ የንጽሕናችንም መሠረት እኛን ስለማዳን ሰው የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል በወለደችልን በድንግል ማርያም ተገኘልን። ሰው ከሆነ በኋላም ፍጹም አምላክ ነው ስለዚህም በድንግልና ወልደችው። ድንቅ የሆነ የመውለድዋ ችሎታ የማይመረመር ሊነገር የማይቻል ነው።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፪ በእርሱ ፈቃድ በአባቱ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ መጥቶ አዳነን።
፫ በድንግልና ፍጽምት የሆንሽ ማርያም ሆይ የድንግልናሽ ምሥጋናና ክብር ታላቅ ነው።እግዚአብሔር ካንች ጋር ቢሆን ባለሟልነትን አግኝተሻልና።ያዕቆብ ከምድር እስከ ሰማይ ደርሳ የእግዚአብሔር መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት ያያት መሰላል አንቺ ነሽ።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፬ ሙሴ በነደ እሳት ሳትቃጠል ያያት ዕፅ አንቺ ነሽ ይኸውም መጥቶ በማኅፀንሽ ያደረው የእግዚአብሔር ልጅ ነው የመለኮቱ እሳትነት ሥጋሽን አላቃጠለውም።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፭ ዘር ያልተዘራባት እርሻ አንቺ ነሽ የሕይወት ፍሬ ከአንቺ ወጣ።ዮሴፍ የዋጃትና የከበረ ዕንቁን ያገኘባት ሣጥን አንቺ ነሽ።ይኸውም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በማኅፀንሽ አደረ በዚህ ዓለምም ወለድሸው።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፮ የመላእክት ደስታቸው የሆነ ጌታን የወለድሽ ሆይ ደስ ይበልሽ።የነቢያት ዜናቸው ንጽሕት ሆይ ደስ ይበልሽ። እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ቢሆን ባለሟልነትን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ። የዓለም የሰው ሁሉ ደስታ የሆነ የመልአኩን ቃል ተቀብለሻልና ደስ ይበልሽ።ዓለምን
ሁሉ የፈጠረ ጌታን የወለድሽ ሆይ ደስ ይበልሽ።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፯ በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ።የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ
ይበልሽ።ፍጥረቱን ሁሉ የሚመግበውን እሱን ጡትሽን አጥብተሽዋልና ደስ ይበልሽ።የሕያዋን (የጻድቃን) ሁሉ እናታቸው ቅድስት ሆይ ደስ  ይበልሽ። ትለምኝልን ዘንድ ወደ አንቺ እናንጋጥጣለን።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፰ ድንግል ሆይ ቅድስት ሆይ ጌታን የወለድሽ ሆይ እኛን ለማዳን ድንቅ ምሥጢር (ተዋህዶ) በአንቺ ቢደረግ ንጉሥን ወልደሽልናልና ፍጥረታትን በልዩ ልዩ መልክ የፈጠረ የእርሱን የገናንነቱን ነገር ፈጽመን መናገር አይቻለንምና ዝም እንበል።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፱ ወደ ደብረ ሲና የወረደ ለሙሴ ሕግን የሰጠ የተራራውን እራስ በጽጋግ በጢስ በጨለማና በነፋስ የሸፈነ ፈርተው የቆሙትንም በነጋሪቶች ድምፅ የገሠፀ የአብ አካልዊ ቃል ነው።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፲ በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ ይኸውም ወደ አንቺ የወረደው ነው።ሰውን የወደደ እርሱ ያለመለወጥ ባንቺ ሰው ሆነ።እንደ እኛ በሚናገር ሥጋ ፍጹም ሆኖ አምላክ በመንፈስ ቅዱስ በማህፀኗ አደረና ፍጹም ሰው ሆነ።አዳምን ያድነው ዘንድ ኃጢአቱንም ያስተሠርይለት ዘንድ በሰማያት (በሰማያዊ መዓርግ) ያኖረው ዘንድ በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ወደ ቀድሞው ቦታው ይመልሰው ዘንድ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
፲፩ የድንግልን ገናንነቷን ሊናገሩት አይቻልም።ጌታ መርጧታልና የሚቀርበው በሌለ ብርሃን ውስጥ የሚኖር እርሱ መጥቶ አደረባት ዘጠኝ ወር በማኅፀንዋ አደረ የማይታይና የማይመረመር (ታይቶ የማይታወቅ) እርሱን በድንግልና ወለደችው።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፲፪ ነቢዩ ዳንኤል ያየው ያለ እጅ ከረጅም ተራራ የተፈነቀለው ያ ደንጊያ ከአብ ዘንድ የወጣው ቃል ነውና መጥቶ ያለወንድ ዘር ከድንግል ተወልዶ አዳነን።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፲፫ እንደ ንጹሕ ጫፍ ሆንሽ የሃይማኖትም መገኛ ነሽ የቀናች የቅዱሳን አባቶቻችን ሃይማኖታቸው ነሽ። አምላክን የወለድሽና በድንግልና የታተምሽ ንጽሕት ሆይ የአብን ቃል ወለድሽልን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን መጣ።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፲፬ የከበርሽ ጌታን የወለድሽ ሆይ የማይታይ ቃልን የተሸከምሸው የብርሃን እናቱ አንቺ ነሽ። እሱን ከወለደሽው በኋላ በድንግልና ኖረሻልና በፍጹም ምስጋና ያገኑሻል።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፲፭ የአብ ቃል እናቱ ንጽሕት ድንግል ሆይ ስለ አንቺ የሚነገረውን ነገር መናገር የሚቻለው ምን አንደበት ነው፤ ኪሩቤል ለሚሸከሙት ንጉሥ ዙፋኑ (ማደሪያው) ሆንሽ የተከበርሽ ሆይ እናመሰግንሻልን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ መልካሟ ርግብ ሆይ ስምሽን በልጅ ልጅ እንጠራለን።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

፲፮ እናትና ገረድ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ።የታቀፍሽውን መላእክት ያመሰግኑታል ኪሩቤልም በፍርሃት ይሰግዱለታልና ሱራፌልም ያለማቋረጥ ክንፋቸውን ዘርግተው የሚመሰገን ንጉሥ (የክብር ባለቤት) ይህ ነው፤ በይቅርታው ብዛት የዓለምን ኃጢአት ያስተሰርይ ዘንድ የመጣው ይህ ነው ይላሉ።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

Loading comments...