🛑ሼህ ኢብራሒም ሐኪም (እነሸህ ጎሌ ኤጀርሳ) ረሒመሁሏህ,ታላቁ የቁርአን ተፍሲር አባት!

2 years ago
1

ወረባቦን በሀገር አቀፍ ደረጃ እንድትታወቅ ካደሩጉ  በእስልምና ሀይማኖት አስተምህሮ በቁርአን ተፍሲር ገነው ከሚታወቁ የሀይማኖት መምህር አንዱ ነበሩ ሸህ ጎለጀርሳ (ሸህ እብራሂም ሀኪም)

ሸህ እብራሂም ሀኪም በወረባቦ ወረዳ 019 ቀበሌ ጎለጀርሳ ተወለዱ እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ እንደ ማንኛውም የእስልምና ሀይማኖት ተማሪ ወደ ሰፈር በመውጣት የቁርአን ትምህርታቸውን በቃሉ ወረዳ እርጎየ አካባቢ ቀሊና መንደር በመከታተል ጀመምረው በተለያዩ ቦታዎች በመንቀሳቀስ  ትምህርታቸውን ተከታትለው እስከ ሸህነት ደርሰዋል።

የመማር ጊዜያቸውን አጠናቀው የሸህነት ማእረግ ሲያገኙ  ወደ  ትውልድ ቀያቸው በማምራት የቁርአን ተፍሲር ማቅራታቸውን ጀመሩ።   በዚያም በመቀጠል በምሽንጋ ለ6 አመት አድስ አበባ ለ1 አመት እንድሁም በቢስቲማ ፉርቃን መስጅድ ለ6 አመታት ያክል የቁርአን ተፍሲርን ያቀሩ ሲሆን በመጨረሻም ወደ ጎለጀርሳ በመሄድ ማቅራታቸውን ቀጠሉ

ደረሶች በጎለጀርሳ ሀሪማ ከመላ ኢትዮጵያ በመምጣት የቁርአን ተፍሲር ቀርተዋል። በሀገራችንም ብዙ የኢስላም ሊቃውንት አፍረተዋል፣ አነሰደበታቸው ጣፋጭ ሰው ወዳጅ መልከ መልካምና ለደረሶቸው የሚተናነሱ፤ ደረሳ ጋር ባላቸው ቀረቤታ በደረሶቸዎ ዘንድ ተወዳጅ ነበሩ

ሸህ ጎለጀርሳ በተለያዮ ቦታዎች ከ 65 አመት በላይ የቁርአን ተፍሲርን አስተምረዋል።

ሸህ ጎለጀርሳ ባደረባቸው ህመም ጥቅምት 25 ምሽት ላይ ከዚህ አለም በሞት የተለዮ ሲሆን የቀብር ስነ ስርአታቸው  ወዳጅ ዘመዶታቸውና ደረሶቻቸው በተገኙበት በጎለጀርሳ በዛሬው እለት ይፈፀማል።
*.       ጎሎ-ጀርሳ የትምህርት ማእከል.       **
               ሼይህ ኢብራሂም ሓኪም!
                            ወረባቦ | ወሎ

  ኢትዮጵያ አንድ የቁርአን ተፍሲር ሊቋን አጣች!

በአማራ ክልል ደ/ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ቀበሌ 19 ከቢስቲማ 22 ኪሜ አካባቢ፣ ከደሴ ደግሞ 69 ኪሜ እርቀት ላይ የሚገኝ  መንደር ነው፡፡

ማእከሉ በሼይህ ጎሎ ጀርሳ ይታወቃል:: ከ5 መቶ በላይ ታላልቅ ምሁራን  ያፈራ ታላቅ የተፍሲር/"የቁርአን ትንታኔ ትምህርት" ማእከል ነው::

ማእከሉ የተመሰረተው በትልልቅ ምሁራን የተሞላ ቤተሰብ ነው፡፡ ሼይሁ ቁርአን የተማሩት በትውልድ መንደራቸው እርጎዬ ቀሊና መንደር በሸይኽ ሑሴን መሕሙድ ለገሂዳ ነው::

ለ10+  ዓመታት ያክል ደግሞ የሐነፊን መዝሃብን ተምረዋል፡፡

"የእረብኛ ትምህርትን"  /ነህውን በሸይኽ ዓብዱ በእርጎዬ ለ5+ዓመት ተምረዋል፡፡

የቁርእን ትፍሲርን ለ 7አመት ያክል: 2 አመት ሸይህ ዳውድ ኢብራሂም ወረሂበኖ ላይ እና  5 አመት ሸይህ ኸሊል አሕመድ ጮሬ ላይ ተምረዋል:: 

ከዚያ በሁዋላ እርጎዬ ላይ በመምህራቸው ተድረው ፊቅህ ያስተምሩ ነበር!

በሁዋላም ወረባቦ ውስጥ የቁርአን ተፍሲርና የፊቂህ ትምህርትን ለ11 + ዓመት ያህል አቅርተዋል፡፡

በመጨረሻም በጎሎጀርሳ  ለ44+ ዓመት ያህል የቁርአን ተፍሲርን አቅርተዋል፡፡

በአጠቃላይ ሸይሁ ቁርአን ተፍሲርን ከ65+ ዓመት በላይ እንዳስተማሩ ይነገራል፡፡ አሁን ግን ያ ሁሉ የእውቀት ማእድ በሼይህየው ሞት ተነሳ!

ከ500 እስከ 800 የሚቆጠሩ ምሁራንን ያፈሩት ሸይህ ጎሎጀርሳ ፍሬወቻቸው በጎንደር፣ በጎጃም፣ በሸዋ፣ በትግራይ፣ በወለጋ፣ በዓፋር በመላው ሀገሪቱ ተበትነው በማስተማር ላይ ይገኛሉ፡፡

ከተማሪወቻቸው መካከል:-
       ሼይህ ኢብራሂም ወረሂመኖ (ወለጋ ላይ)
       ሼይህ ሑሴን ጠፋ (ሂዲ ላይ)
       የፊቂህ ሊቁ ሼይህ ቁኑ ፣
        የነሕውና ተፍሲር ሊቁ ሼይህ ሙሐመድ ያሲን፣
        የፊቅህ ሊቁ ሼይህ አሕመድ ሙስጠፋ ሓጣይ፣
        ሸይኽ ሙሐመድ መነዮ፣
        ሸይኽ ሙሐመድ መጊት፣

            አላህ ስራቸውን ይቀበላቸው።
#quran #yasinnuru #ሰበር

Loading comments...