Ethio 360 በሰላም ይረፉ ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በብሩክ ይባስ

3 years ago
7

የክፍለ-ዘመናችን የሰብአዊ መብት ተሟጋች፣ ደራሲና ልሒቅ የሆኑት ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም ዜና እረፍት መስከረም 19 ቀን 2013 ዓ.ም. ከተሰማ ጀምሮ ኢትዮጵያዊያን በከፍተኛ ሐዘን እንዲዋጡ አድርጓል።
አገራችን በገባችበት አጣብቂኝ ወቅት እንደ ፕሮፌሰር መስፍን ያሉትን የአገር ዋርካዎች ማጣት ለኢትዮጵያ መሪር ሃዘን ነው።

ለማንም ግልጽ ሆኖ እንደሚታወቀው የአደባባይ ምሁር የሆኑት ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም ለሶስት ተከታታይ ትውልዶች ያህል በቆየ የምሁራዊና ሰብዓዊ አገልግሎታቸው በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ከፍተኛ ስፍራ በመያዝ ትውልድ የማይረሳው አሻራ አኑረዋል።

Loading comments...