የፓስተሮች ጉድ | መንሱር ጀማል ስለሚስቱ | ትዳር | ነብዩን (ሰዐወ)በህልም ማየት #salman_media #nejah_media

2 years ago

(የምስክርነት ቴክኒክ)
..
❝.. አቡ ሀይደር አንተ ክርክር ምን ያደርግልሀል? እግዚአብሄር እውነቱን ገልፆልሀል አይደል?..❞
..
ወንጌላውያን ሙስሊሞችን መሳብ እንችላለን ብለው ከሚጠቀሙባቸው መንገዶች ውስጥ አንዱ የምስክርነት መንገድ ነው። የዚህ መንገድ ዋነኛ ሚና እስልምናን ክደናል የሚሉ የሆኑ ግለሰቦችን በምሳሌነት በማሳየት "ኑ እናንተም" የሚሉበት መንገድ ነው። በዚህ መንገድ ተርታው ሙስሊም ላይ ብዥታን በመልቀቅ ከእስልምና ለማፍለስ ይሞክራሉ። በዚህ መንገዳቸው ውስጥ ግን እግረመንገዳችንን ልናውቃቸው የሚገቡ መሠረታዊ ነጥቦች አሉ።
..
❐ የመጀመሪያውያ ነጥብ ለምስክርነት የሚመርጧቸው ሰዎችን በተዛባ ወይንም በውሸት ማንነት ይቆልሏቸዋል። ግለሰቦቹ ተራ አማኞች ሳይሆኑ በእስልምና ውስጥ ትልቅ ቦታ የነበራቸው ዓሊሞች ወይንም ኡስታዞች እንደነበሩ አስጩኸው ይነግሯችኃል። አንዳንዴ ሲዋሹ እራሱ ልክ አያውቁም። በአንድ ወቅት አንዱ አንዋር መስጅድ ኢማም ነበርኩ ብሎ ግነቱን ገደብ ሲያሳጣው አይቸ ለሱ አፍሬያለሁ። መሠል ሰዎች በእምነቱ አማኞችም ጭምር ስለማይጠየቁና ክሮስ ቸክ ስለማይደረጉ እንደፈለጉ መዋሸት ይችላሉ። መድረክ የሰጧቸው ሰዎችም እየዋሹ እንደሆነ እንኳን ቢያውቁ ለሚሲዮናዊ አላማቸው እስከጠቀማቸው ድረስ ውሸቱ አያስጨንቃቸውም።
..
❐ በተመሳሳይ ደግሞ አንዳንድ ሙስሊም ነበሩ በሚል የሚያመጧቸውን ሰዎች ከበሽታ መዳን ጋር በማያያዝ "ተዓምር" እንደተሰራላቸው በመግለጽ እንዲያማልሉ ሊያደርጉ ይችላሉ። ሚስኪኑ ህዝብ በተለይም ህመምና ጭንቀት ያለበት ኢማኑ ደከም ያለ አማኝ በወጥመዳቸው ውስጥ ሊወድቅ ይችላል። በዚህ መንገዳቸው አንዳንዴ ሲህር በመጠቀም አንዳንዴ ደግሞ የብር እርዳታም በማድረግ ሰውየው ከህመሙ እንዳገገመ እንዲሰማው ብልጠትም ሊጠቀሙ ይችላሉ። ይህ በአብዛኛው ገጠር አካባቢ የሚሰሩት መንገድ ሲሆን አሁን ደግሞ "የነብያት ጸጋ" በተሰኘው የ"አገልግሎት" መንገድ የሚያምኑ ፕሮቴስታንቶች በቴሌቭዥን ጭምር ይጠቀሙበታል።
..
📌 የግል ገጠመኞቼ
..
ሙስሊም ነበርኩ በሚል በርካታ ሰዎችን በማኅበራዊ ሚዲያ በኩልም በአካልም የማግኘት ተሞክሮው ገጥሞኛል። በዚህ ሒደት ውስጥ የታዘብኩት ነገር ሙስሊም ነበርን በሚል መጠቀሚያ የሆኑ ሰዎች ከሚከተሉት ተርታ ውስጥ የሚመደቡ ናቸው፦
.
1/ ፈጽሞ ሙስሊም ያልነበሩ ግን ስክሪፕት በማጥናት እንደ ሙስሊም መተወን የስራ ክፍል ተደርጎ የተሰጣቸው ሰዎች
..
2/ በስም በእርግጥም ሙስሊም የነበሩ ነገር ግን በቅጡ እንኳን ቁርአን ያልቀሩ፥ የእስልምና ማዕዘናትን እንኳን ብትጠይቋቸው የማያውቁ ናቸው። ከዚያም በከፋ አንዳንዶቹ ጭራሽ ፋቲሀን እንኳን መቅራት የማይችሉ ናቸው።
..
3/ ድነናል በሚል ቴሌቭዥን ላይ ከቀረቡ ሰዎች መካከል በግሌ ሁለት ሰዎችን ማግኘት ችየ የነበረ ሲሆን ሁለቱም በስተመጨረሻ የነገሩኝ ነገር በመቸገራቸው ምክንያት ብር ተከፍሏቸው መተወናቸውን ነው። እስልምናን አለቀቁም ነገር ግን ብሩ አስፈልጓቸው በዚያ ተግባር ውስጥ መገኘታቸውን ነው። አንዷ እንዴውም በቴሌቭዥን መተላለፉንና በዚያ መታየቷንም ፈጽሞ አታውቅም ነበር።
..
4/ እነዚህኛዎቹ ደግሞ በትክክልም ሙስሊም የነበሩ ነገር ግን በተለያዩ ሹብሀዎች ተታለው ወደ እምነቱ የገቡ ሲሆኑ የሚሰሩት ስራም እውነት መስሏቸው የሚለፉ ናቸው።
..
5/ እነዚህኛዎቹ በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች ተታለው የሄዱ ሰዎች ሲሆኑ በመሠረታዊነት ጥቂት የእስልምና እውቀት ያለቻቸውና ያችኑም በመመንዘር ሙስሊሙን ለማክፈር የሚጥሩ ናቸው። ከነዚህ ሰዎች ጋ በተያያዘ አንድ ወይንም ሁለት የማቃቸው ሰዎች ያሉ ሲሆን በሚስዮናውያን ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ ተደርጎላቸው የራሳቸው ሚንስትሪ ተቋቁሞላቸው የገጠሩን ክፍል ለማክፈር የሚባትሉ ናቸው። ከኡስታዝ አቡ ሐይደር ጋር በነበረን ጨዋታ ከአንደኛው ሰውየ ጋር የነበረውን ገጠመኝ በተመለከተ አጫውቶኝ ነበር። ከሙስሊሞች ሰው አምጡ ብሎ አዳማ ላይ በጠየቃቸው ወቅት ለውይይት ኡስታዝ አቡ ሐይደርን ይዘውት ይሄዳሉ። ከሄዱ በኃላ ሰውየው ኡስታዝ ይመጣል ብሎ አልጠበቀሞ ነበርና ገና ኡስታዝን ሲያየው ተጠግቶ ያለው አንድ ነገር ብቻ ነው፦
.
❝.. አቡ ሀይደር አንተ ክርክር ምን ያደርግልሀል? እግዚአብሄር እውነቱን ገልፆልሀል አይደል? ❞ ሲል ለኡስታዝ አቡ ሐይደር ነግሮታል። ኡስታዝ ሰውየው እንዴት አኼራውን ለተራ ዱንያ ነገር ይሸጣል? የሚለውን ነግሮት መለያየታቸው ገልጾልኛል። እነዚህ ሰዎች አሁን ድረስ ሳውቃቸው የሚነዱት መኪና እጅግ ዘመናዊ ሲሆን በዱንያ በኩል ያልተጓደላባቸው ናቸው። ነገር ግን ከአኼራቸው ዱንያቸው በለጠባቸውና ስሜታቸውን "አምላክ" አደረጉ።
.
أَرَأَيْتَ مَنِ اتَّخَذَ إِلَـٰهَهُ هَوَاهُ
.
📌 ሲጠቃለል
.
በተለያዩ አጋጣሚዎች በሀገራችንም ሆነ በውጭው አለም "ምስክርነት" ተብለው የሚቀርቡ ግለሰቦችን ስትመለከቱ ከላይ ካነሳኃቸው ነጥቦች የሚዘሉ አይደሉም። ከሞላ ጎደል ብዙዎች የገንዘብ ሰው ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ለማታለያነት መጠቀሚያ የሆኑ ናቸው። ይህ መንገድ ግን ብዙ ሙስሊምን ያስኮበለለ አሁንም ድረስ አገልግሎት ላይ እየዋለ ያለ አደገኛ መንገድ ነው።
___

Loading comments...