BLACK PANTHER : ቁርስ ከማብላት እስከ ትጥቅ ትግል | እነዚህን አይቶ ማይኮራ ጥቁር ይኖር ይሆን⁉

2 years ago
9

" its time to fight back that's Huey said"
#Black_Panther
(ቁርስ ከማብላት እስከ ትጥቅ ትግ" k time to fight back that's Huey said.ል) እነዚህን አይቶ ማይኮራ ጥቁር ይኖር ይሆን?

(ቱካ ማቲዎስ)

በ1969 እ.ኤ.አ ትምህርት ከመጀመራቸው በፊት #ጥቁር_ሕፃናትን የአሜሪካ መንግስት ሊያደርግላቸው የልቻለውን ቁርስ የማብላት ፕሮግራም ጀመሩ (ቸኮሌት፣እንቁላል፣ሥጋ፣ፍራፍሬ) ከዝርዝሮቹ ውስጥ ነበሩበት ይሄም ጉዳይ የአሜሪካን መንግስት አላስደሰተም።

#Black_Panther በሚል ስም በውትድርና ውስጥ ባሉና በቆዩ ጥቁር አሜሪካውያን የተቋቋመው ይህ ስብስብ የጥቁርን ነፃነት ያውጃል ለጥቁር መብት ይከራከራል በሚል የሚፈራና እጅግ አስጊ ሆኖ ተገኘ ጋዜጦች የወሬ ርዕሳቸው አደረጉት።በወቅቱ ግን ለህፃናት ብቻ ምግብ ከማቅረብ ውጪ አጀንዳ አልነበራቸውም።

“The #children, many of whom had never eaten #breakfast before the Panthers started their program,” ብሎ ነበር the Sun Reporter.

በ #FBI ያልተወደደውን ይህን በጎ ስራ ማጠልሸትና አባላቶቹን ለማሰር የተጠቀሙበት ወራዳው ተግባር  ምስኪን ህፃናት የሚመገቡትን ምግብ መመረዝ፣ እንዲታመሙ ማድረግና፣ ፓርቲውን ማሳጣት፣አባላቱን አድኖ ማሰር ነበር።ከማሰራቸው በፊት አንዲት የፓርቲው አባል ያደረጉትን ፀያፍ ድርጊት እንዲህ ብላ መስክራለች  “the Chicago #police broke into the church and mashed up all the food and urinated on it.” ምግብ ላይ ርኩስ ሽንታቸውን ሸንተውበታል ባጭሩ።

ከ 1969-1970'ዎቹ የቆየው የቁርስ ፕሮግራም ለአሜሪካ መንግስት free brakefast መጀመር መሰረት ጥሏል።

Black panther party ሲቋቋም ፖሊስ በጥቁሮች ላይ የሚያደርሰውን ጫና ህብረተሰቡን በማንቃትም ሆነ የህግ አግባብ በመጠቀም ማስቆም ነበር አላማው። በኃላ ማህበራዊ ጉዳዮችንም ጨምረውበታል።

ከ1975 በኃላ ድጋሚ ፍቃድ አግኝቶ አሁን አሜሪካ ውስጥ ከት/ቤት በፊት 14.57 ሚልየን ህፃናትን ቁርስ ይመግባል።

የBlack Panther አባላት በዕቡህ የሚንቀሳቀሱና እጅግ የሚፈሩ የሰለጠኑ፣የተደራጁ፣ ታጣቂዎች አሉበት እነሱንም ለመቀላቀል ጥቁር አሜሪካውያን ወጣቶች ይጓጓሉ መቀላቀሉ ግን ቀላል አይደለም። ስማቸውንም ያገኙት #ከጥቁር_ግስላ ባህሪና ፀባይ በመነሳት ሲሆን በጥቅጥቅና ጨለምለም ባለ ደን ውስጥ ሚኖር፣እጅግ የበዛ ሜላኒን ያለው(የቆዳ ቀለም ሚወስን ንጥረ ነገር )፣እጅግ የሚፈራ ኃይለኛ፣ተራራ ቧጥጦ የፈለገበት ሚደርስ፣ፍርሃት የማያውቅ፣ቁጡ፣ ከእይታ ተሰውሮ ታዳኙን የገባበት ገብቶ ከሚያድን እንስሳ ነው።

#2_pac_Change በተባለው ዘፈኑ ከብላክ ፓንተር  መስራቾች አንዱን #Huey p.Newton'ን (ገድለውታል) በማንሳት " k time to fight back that's Huey said.
ሲል አወድሶታል።ስለዚህ ድንቅ #ጥቁር_ሰው አንድ ቀን እናወራለታለን።

#2pac #ethiopia #NoMore #

የሃገራችን ሙዚቃ አቀንቃኝ አለማየሁ እሸቴ #ያ_ጥቁር_ግሥላ በሚለው ዘፈኑም
ጥቁር እንደንስሳ የተቆጠረበት፣
አልገባንም እኛ ብናውቅ ምንአለበት::
እያለ ሳያነሳቸው አልቀረም።

ሰሞኑንም በሴት ኮማንደር የሚመራ የዕቡህ አካል የሆነው #የብላክ_ፓንተር ግሩፕ በተቃውሞ ሰልፍ ላይ ታይቶ መነጋገሪያ ሆኗል።አሜሪካ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ዓለም ክፍሎች ላይ ይንቀሳቀሳል በጥቁር ልብሳቸው በተክለ ሰውነታቸው ዳንስ መሰል እንቅስቃሴያቸው ይለያሉ።
(ነጽሩ ወዘሠናየ አጽንዑ)

#ethiopia #world #usa #africa #haileselassie

Loading comments...